አብዛኛው ጫት ቤት ተጠቃሚ ለምን ጫት ቤት እንደሚሄድ ብትጠይቁት የሚሰጣችሁ ምላሽ ተቀራራቢ
ነው፡፡ ጫወታው ይመቻል ነው፡፡ እውነትም ጫት ቤት ለየት ባለ መልኩ ከሁሉም የስራ ዘርፍ የተለያዩ ሰዎችን ማግኘት የተለመደ ነው፡፡ አስተማሪው ፡መሃነዲሱ
፡ ሀኪሙ ደላላው ፡ ቀፋዩ ፡ፖሊሱ ፡ ሌባው በአንድነት የሚገናኝበት
ቦታ ነው፡፡
ታድያ እነዚህ ጫት ቤት ውስጣ የማይጠፉ ወሬ አዋደው የሚያወሩ ፡ በአብዛኛው በቅፈላ ስራ
የተሰማሩ አጫዋቾች አሉ፡፡ እነዚህ አጫዋቾች ወደ ጫት ቤት የሚገቡት ቤሳቤስቲን ሳይዙ ነው፡፡ ከተገኘ ከታዳሚዎቻቸው ካልሆነም ከ
ባለጫት ቤቶቹ በማይከፈል ዱቤ ይቅማሉ፡፡ አላማቸው ማሳቅ ነው፡፡ ስለዚህ እነሱጋ ስርአት ብሎ ነገር የለም፡፡ ደጋግሞ የሚጋብዛቸው
የገባው፡ ያራዳ ልጅ ፡ አሪፍ ፤ የሚሉት ስሞች ይወርድለታል ፡፡ ሠላምም ሲሉ በተለሳለሰ አጨባበጥ ፡ በአብዛኛው ከመቀመጫቸው ተነስተው
ነው፡፡
የማይፈለጠው የራሱን ቅሞ የሚሄደው ግን በአብዛኛው ፡ ያልገባው፡ ጤባ ፡እርጥብ ፡ አቦ
ይሄ ሰው አይመቸኝም ….የመሳሰሉት ቃላት ይወደወሩበታል፡፡
ብዙ ግዜ የሚገርመኝ የጫት ቤቶቹ ደረጃ እና የሚገቡበት ሰዎች አለመጣጣማቸው እና ይህንንም
ሰዎቹ አለማስተዋላቸው ነው፡፡ ለነገሩ ከቦታው ሳይሆን ትልቁ መፈላለግ ያለው ከሰዎቹ ነው፡፡ በተለይ አባዛኛዎች የጥበብ ሰዎቻችን
ስለጥበብ ጫት ቤት ካልሆነ ማውራት አይመቻቸውም( ታድያ እዚህ ጋ አብዛኛው ማለቴ ይሰመርልኝ፡፡ ይሀው ችግር ያስቸገራቸው እና አጋር
ያጡ ጠንከር ያሉ ጥበበኞች እንዳሉ ልብ ይሉዋል፡፡)
ጫት ቤት ውስጥ የማያወራ የወግ ርእስ የለም፡፡ ስለፍቅር፡ ስለትዳር፡ ስለኑሮ ውድነት፡
ስለ ጥበብ፡ ስለግድብ፡ስለስደት ፡ ኩዋስ፡ ተቃራኒ ጾታ፡ ፖለቲካ ፡ እንዲሁም ፡ ስለአዳዲስ ክስተቶች… በሙሉ ይወራል፡፡
ታድያ ደስ የሚለው ስለሚወራው ርእስ በቂ እውቀት ይኑረውም አይኑረውም ሁሉም ስለ ሁሉም
ነገር ያወራል፡፡ አለማውራት የሚያስቀጣ እስኪመስል ድረስ ይወራል፡፡
ሚርቃና የ መቃም የክላይሜክስ ጥግ ሲሆን አብዛኛው ሰው ጫትን የሚቅመው ይህንን ደረጃ
ለመንካት ነው፡፡ ታድያ የየሰዉ የሚርቃና አይነት ይለያያል፡፡ አንዳንዱ ሲመረቅን ስለተለያዩ ሀሳቦች በበለጠ ማውራት ሲፈልግ አንዳንዱ
ጭራሽ አብሮት ሲቅም የነበረውን ሰው ጥርቅም አድርጎ ይዘጋዋል፡፡ አንዳንዱ የፈጠጠ አይኑን እያቁለጨለጨ አካባቢውን ይመለከታል፡፡
በጣም ወጣ ያሉ የሚርቃና አይነቶችም ይስተዋላሉ፡፡ ከነዚህ ውስጥ ለየት ያሉትን ላንሳ
- አንዳንዶች ሲበዛ ቸር ይሆናሉ ከመርቀናቸው በፊት ወይ ፍንክች ይሉ የነበሩት ፡ ከሚርቃና በሁዋላ ያልመረቀነ ሰው ካዩ ጫት ካልገዛን
ብለው ያስቸግራሉ፡፡ የለባቸው ዱቤ አንድ በአንድ ትዝ ስለሚላቸው ካልከፈሉ ወይ ኪሳቸው ያለው ብር ካላለቀ ምንም እርካታ የላቸውም፡፡
አንድ በጣም የሚያስቅ ሚርቃና ያለው ሰው ደግሞ ሁሉንም ቀዳዳዎቹን መዝጋት ይጀምራል፡፡
ብርድ እንዳይመታው መሆኑን ስትሰሙ ፈገግ ያድርጋል፡፡
የጫት ተጠቃሚ ሴቶች ቁጥር እንደወንዱም ባይሆን ትንሽ የማይባል ሆኑዋል፡፡
ጫት ቤት በብዛት የሚሰማ ነገር ቢኖር የሚራዘም ቀጠሮ ነው፡፡ ምን ባክህ ቤተሰብ ጋር
ሄጄ ሳልመለስ ቀረው ፡ በጣም ሩቅ ቦታ ነኝ ነገ እናድርገው፡፡ ….የመሳሰሉትን ንግግሮች መስማት የተለመደ ነው፡፡
ብዙዎች እነደሚናገሩት ጫት የሚጀምሩት በጉዋደኛ ግፊት ሲሆን ወደ ሱስነት መቀየሩን መቀበል
ይከብዳቸዋል፡፡ በብዛት ማቆም ቀላል መሆኑን ግን ግዜኣቸውን የሚያሳልፉበት ሌላ ቦታ እንደሚያጡ ያስረዳሉ፡፡ ከዚህም በላይ ጫት
ምንም አይነት የጤና ጉዳት እንደሌለው አጥብቀው ይከራከራሉ፡፡
የጫት ሱሰኝነትን የበለጠ የሚያስረዳልኝ ማመላከቻ አንድ ጉዋደኛዬ ነው ፡፡ ይሀው ጉዋደኛዩ
የ ፋርማሲ ዲግሪውን ሲያጠናቅቅ የስራው ጫት በጤና ላይ በተለይ በወሲብ ህይወት ላይ ያለውን አሉታዊ ተጽእኖ ሲሆን ያቀረበው ጽ
ሁፍም በአስተማሪው ተወዶለት ጥሩ ውጤት አስገኝሎታል፡፡ አስተማሪውም በጽሁፉ ያልተሸፈኑ ሌሎች ጥናቶችን እነዲያከናውኑ ሌሎች ተማሪዎችን
ይገፋፋሉ ፡፡ ታድያ ይህ ጉደኛዬ ጥናቱን ሲያከናውም ሆነ ጥናቱን ከጨረሰ በሁዋላ በአቃቃሙ ላይ ምንም ለውጥ አላሳየም፡፡ ይልቁኒም
ጨመረበት እንጂ፡፡
ቸር እንሰንብት!!