Saturday, January 30, 2016

የአረብ ሀገር ሴቶቻችን እና የፍቅር ጫወታ!!





በቅርብ አንድ ወዳጄ ከቅርብ ግዜ ወዲህ ቢዚ ቢዚ ሲያበዛብኘን እንዲሁም የኑሮው ሁኔታ ለውጥ ሲያሳይ፤ ከወትሮው ብድር ጥያቄው ቀነስ ቢያደርግብኝ ፡ ተገናኘተን ስለለውጡ ለመነጋገር ተስማማን-
ስንገናኝ ሰላምታ ከተለዋወጥን በሁዋላ- አንድ ነገር አስተዋልኩ - የሚገርም ሳመሰንግ ስልክ ገዝቱዋል፡፡-ከስልኩጋም የተለየ ዝምድና ፈጥሮል፡፡
የዚህ ለውጥ ነገር ሚስጥሩን ለማወቅ -በጥያቄ ጀመርኩ "ምን ተገኘ ባክህ እንዲህ የጠፋሀው ? ደሞ ውበቱን ደፍቶብሃል!!"
"ምን ባክህ ጊዜ ጠፋ" - አለኝ ስልኩን እየነካካ
የስልኩን አዲስነት እና ጥሩነት እያደናነቅኩኝ ምን አዲስ ነገር እንደተገኘ ጠየኩት፡፡
አዲስ የስራ ዘርፍ እንደተገኘ ና በጣም አዋጭ እና ቀላል እንደሆነ የሚያስፈልገውም ስልክ ብቻ መሆኑን ነገረኝ፡፡ የሚነግረኝ ነገር የበለጠ ለመወቅ የሚያጉዋጋ በመሆኑ የበለጠ እንዲነግረኝ ጋበዝኩት
ስራው የሚሰራው በቫይበር እነደሆነና ወጪው የቴሌ ካርድ መሆኑን እርሱም ቢሆን በደንበኞቹ እንደሚከፈል ነገረኝ፡፡ ጉዳዩ የበለጠ ስላጉዋጉዋኝ  የስራውን ምንነት እንዲነግረኝ ጠየኩት

"ሥራውማ ከ አረብ ሀገር ሴቶች ጋር ፍቅር መስራት ነው!! "አለኝ፡፡ ነገሩ ግልፅ ስላልሆነልኝ እንዲያስረዳኝ ጠየኩት፡፡
"ምን መሰለህ "- ቀጠለ -"በአብዛኛው የ አረብ ሀገር ሴቶች ለብዙ ግዚያት ታፍነው ነው የሚቆዩት ፡፡ ስለዚህ ስለፍቅር ስለወሲብ በደምብ የሚያወራቸው ሰው ይፈልጋሉ፡፡ ስለዚህ መጀመርያ የሚስብ ቁመና ያለው ምስል የያዘ የፌስቡክ አካውንት ትክታለህ ፡፡ ከዚያም በየሀረብ ሀገር ያሉ ሴቶችን ታጠምዳለህ፡፡ ሁሉም ሴቶች እኩል ላየፈልጉ ይችላሉ፡፡ አንዳንዶች ስለሀገር ማውራት ይወዳሉ ፡፡ አንዳንዶች ስለሀያማኖት ማውራት ይወዳሉ ፡፡ አብዛኛዎቹ ግን ስለ ስክስ ማውራት ይወዳሉ፡፡ ስለሴክስ የሚያወሩት ግን እስከመጨረሽያው ነው ፡፡ አብዛኛዎቹ የስልክ ሴክስ ማድረግ ይፈልጋሉ ፡፡ ቢያንስ በሁለት ቀን አንዴ የስልክ ሴክስ መድረግ ትፈልጋለች ስለዚህ የኔ ስራ እነሱን መርዳት ነው ፡፡ ከዛማ የ ምትፈልገውን መጠየቅ ነው ይደረግልሃል፡፡ የሚገርምህ አንዳንዶቹ ሀገር ቤት ጉዋደኛ አላቸው ግን የሚያወሩዋቸው ስለ ቤት ጣጣ ነው እንጂ ስለሴክስ አይደለም፡፡ ስለዚህ ለኛ ለኛ ተመችቶናል፡፡" እያለ ያስረዳኝ ጀመር፡፡
"ቾቤን ታውቀው የለ ያ የላይ ሰፈሩን ልጅ ፣ ሰሞኑን 5 ል ታክሲ ሊገዛነው ፡፡ ባርያው ጫት ቤት የከፈተው ኬት አምጥቶ ይመስልሃል?"
ከውስጤ አዘንኩ፡፡ ሴቶቻችን ይህንን ገንዘብ ለማመጣት የሚከፍሉትን መስዋትነት አሰብኩና የምር ከውስጤ አዘንኩ፡፡

No comments:

Post a Comment